የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ መንደር የውስጥ ለውስጥ የአስፓልት መንገድ ግንባታ
አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 7 ቀን 2018 ዓ.ም፡- የአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ባለሥልጣን፤ በገላን ጉራ ኢንዱስትሪ መንደር የአስፓልት መንገድ ግንባታ በማከናወን ላይ ይገኛል።
በባለሥልጣን መሥሪያ ቤቱ የራስ ኃይል እየተገነባ የሚገኘው ይህ የውስጥ ለውስጥ መንገድ በአጠቃላይ 1.3 ኪሎ ሜትር ርዝመት የሚሸፍን ነው፡፡
አሁን ላይ ሰቤዝ የማንጠፍ ስራ እየተከናወነ የሚገኝ ሲሆን፤ የመንገድ ግንባታው ሙሉ ለሙሉ ሲጠናቀቅ፤ የኢንዱስትሪ መንደሩ የሥራ እንቅስቃሴ እንዲቀላጠፍ ከፍተኛ አስተዋፅኦ እንደሚያበረክት ይጠበቃል፡፡
የፕሮጀክቱን ቀሪ ሥራዎች በፍጥነት ለማጠናቀቅ እየሰራ መሆኑን የባለሥልጣን መስሪያቤቱ የደቡብ መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት ጽ/ቤት አስታውቋል፡፡


Previous Post
Next Post
Users Today : 19
Users Last 7 days : 186
Users Last 30 days : 880