ለትራፊክ ፍሰት ምቹ ያልሆኑ መንገዶችን በመለየት ጥገና እየተከናነወነ ይገኛል፡፡
አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 26፣ 2015 ዓ.ም፡- የአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ባለስልጣን በአገልግሎት ጫና፣በአጠቃቀም ችግርና በሌሎች ተያያዥ ምክንያቶች በከተማዋ የተለያዩ ቦታዎች ለብልሽት የተዳረጉ መንገዶችን በመለየት የጥገና ስራ እየተከናወነ ይገኛል፡፡
የጥገና ስራዎች በአብዛኛው በሌሊት ክፍለ ጊዜ የሚከናወኑ ሲሆን ይህም የትራፊክ ፍሰት እንዳያስተጓጉል ያለመ ነው፡፡
በያዝነው ሳምንት ከአፍንጮ በር – ደጃች ውቤ ሰፈር – አራዳ ጊዮርጊስ እንዲሁም ከሞላ ማሩ ወደ አብነት የሚሰደውን መንገድ ጨምሮ በሌሎች አካባቢዎች የአስፋልት የጥገና ስራ ተከናውኗል፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ማህበራዊ ትስስር ገፆችን ይቀላቀሉ
ቴሌግራም:- https://t.me/AddisRoads
ፌስ ቡክ :- https://www.facebook.com/AbabaCity
ትዊተር :- https://twitter.com/AbabaCity
ኢንስታግራም፡- https://www.instagram.com/addisababaroads/
