ከዋቢ ሸበሌ ሆቴል ወደ ቡና እና ሻይ የሚያቋርጥ መንገድ ተገንብቶ ለትራፊክ ክፍት ተደርጓል
የካቲት 12 ቀን 2018 ዓ.ም፣ አዲስ አበባ፡- የአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ባለሥልጣን፤ ከዋቢ ሸበሌ ሆቴል ወደ ቡና እና ሻይ የሚያቋርጥ የመንገድ ግንባታ ስራ አጠናቆ ለአገልግሎት ክፍት አድርጓል፡፡
ባለሥልጣን መስሪያ ቤቱ፤ በዋና ዋና መንገዶች ላይ የሚፈጠረውን የትራፊክ ጫና ለማቃለል፤ በተለያዩ አካባቢዎች ዋና ዋና መንገዶችን በአጭር ርቀት የሚያስተሳስሩ አቋራጭ መንገዶችን በመገንባት ላይ ይገኛል፡፡
በቅርቡ የግንባታ ስራው ተጠናቆ ለአገልግሎት ክፍት የተደረገው ይህ መንገድ 180 ሜትር ርዝመት እና የእግረኛ መንገድን ጨምሮ 15 ሜትር የጎን ስፋት አለው፡፡
የመንገድ ግንባታ ሥራውን የባለሥልጣን መስሪያ ቤት የማዕከላዊ አዲስ አበባ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት ጽ/ቤት አከናውኖታል።


Previous Post
Next Post
Users Today : 0
Users Last 7 days : 279
Users Last 30 days : 1203