+251 11371 2982 aacracom@gmail.com

ሣምንታዊ የመንገድ ጥገና መረጃ

መስከረም 19 ቀን 2018 ዓ.ም፣ አዲስ አበባ ፡- በተለያዩ የከተማዋ ክፍሎች ጉዳት የደረሰባቸውን መንገዶች በመጠገን ለትራፊክ እንቅስታሴ ምቹ የማድረግ ስራ ተጠናክሮ ቀጥሏል፡፡

በሣምንቱ ጥገና ስራ ከተደረገላቸው መንገዶች መካከል ከለገሀር – ቂርቆስ፣ ከሰሚት 72 – አራብሳ፣ ከጎሮ – ፊጋ፣ ከቃሊቲ ማሰልጠኛ – አደይ አበባ የሚገኙት መንገዶች የሚጠቀሱ ናቸው፡፡

በቀጣይም በሁሉም የከተማዋ ክፍሎች የሚገኙና ጉዳት የደረሰባቸውን መንገዶች በመለየት ተከታታይነት ባለው የመንገድ ጥገና ስራ ለትራፊክ እንቅስቃሴ ምቹ የማድረጉ ሥራ ተጠናክሮ የሚቀጥል ይሆናል፡፡

Comments are closed.