ከንቲባ አዳነች አቤቤ የነዋሪዎችን የኑሮ ጫናን ለማቃለል የተዘረጋ የበጎ ፈቃድ አገልግሎትን በተመለከተ፦
– በበጀት አመቱ አጋማሽ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ለዘላቂ ልማት ያለውን አስተዋጽኦ ለማሳደግ በሚከናወኑ የሰው ተኮርና የበጎ ፈቃድ ተግባራት 1,197,413 (ከ100% በላይ) የህብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏል።
– በዚሁ መሰረት 24 የተስፋ ብርሃን የምገባ ማዕከል በመክፈት በየቀኑ በአማካይ እስከ 36,000 ለሚደርሱ በቀን አንድ ጊዜ እንኳን ምግብ ለማግኘት የሚቸገሩ ነዋሪዎቻችንን እየመገብን ነው፡፡
– ለአቅመ ደካሞች፣ ለአረጋውያን፣ ለሀገር ባለውለታዎችና በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ ለሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች 3,737(74%) ቤቶችን በመገንባት 20,484 (77%) ቤተሰቦችን ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏል።
– ለ917,829 (ከ100% በላይ) በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ለሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች ማዕድ ማጋራት ተችሏል። በህብረተሰብ ተሳትፎ ለሚሰሩ መሰረተ ልማት ስራዎች ብር 479,361,717.8 እንዲሁም በበጎ ፈቃድ 8,714,683,077 በድምሩ ብር 9,194,044,794.80 ጥቅም ላይ እንዲውል ተደርጓል።


Previous Post
Next Post
Users Today : 15
Users Last 7 days : 200
Users Last 30 days : 1043