+251 11371 2982 aacracom@gmail.com

ከየካቲት 23 ወደ ጀሞ 2 የሚወስድ የአስፋልት መንገድ ግንባታ ተጀመረ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 2 ቀን 2018 ዓ.ም፡-የአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ባለሥልጣን፤ በኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ፣ ወረዳ 2 ከየካቲት 23 ሆቴል ወደ ጀሞ 2 የሚያደርስ አቋራጭ የአስፋልት መንገድ ግንባታ ጀመረ፡፡

ቀደም ሲል ተገንብቶ አገልግሎት ሲሰጥ የቆየው ነባሩ መንገድ የተጎዳ በመሆኑ፤ 940 ሜትር ርዝመት እና እግረኛ መንገድን ጨምሮ 20 ሜትር የጎን ስፋት ያለው መንገድ በአዲስ መልክ እየተገነባ ነው፡፡

አሁን ላይ የአፈር ቆረጣ በመከናነወን ላይ ሲሆን፤ ግንባታ ሥራው መኮንን አንለይ ጠቅላላ ስራ ተቋራጭ እና ሆኖስ ቢውሊዲንግ ኮንስትራክሽን በተባሉ ማህበራት እየተከናወነ ይገኛል፡፡ የፕሮጀክቱ የአስፋልትና ተያያዥ ቀጣይ ስራዎች በባለሥልጣን መስሪያ ቤቱ የራስ ኃይል የሚከናወኑ ይሆናል፡፡

የመንገድ ግንባታው ሲጠናቀቅ፤ ከካራ ቆሬ እና አካባቢው ወደ ጀሞ 2 ለሚጓዙ አሽከርካሪዎች አቋራጭ መንገድ በመሆን፣ በአካባቢው ያለውን የትራፊክ ፍሰት የሚያቀላጠፍ ይሆናል፡፡

Comments are closed.