በአንድ ጀንበር 714.7 ሚሊዮን ችግኞችን በመትከል ከዕቅድ በላይ መሳካቱን ግርማ አመንቴ (ዶ/ር) ገለፁ ።
በአንድ ጀምበር 700 ሚሊየን ችግኞችን ለመትከል ታቅዶ 714.7 ሚሊዮን ችግኞች መተከላቸውን የግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ (ዶ/ር) በሰጡት መግለጫ ገልፀዋል ፡፡
አጠቃላይ 29.7 ሚሊዮን ሕዝብ እንደተሳተፈ የተናገሩት ግርማ አመንቴ (ዶ/ር) ፤ የዛሬው ቀን የኢትዮጵያ ሕዝብ በሕብረት ታሪክ የሠራበት ዕለት መሆኑን ተናግረዋል፡፡
መርሐ ግብሩ እንዲሳካ በማስተባበር እና በመሳተፍ ታሪክ የሰሩ ኢትዮጵያውያንን ሁሉ አመስግነዋል፡፡


Previous Post
Next Post
Users Today : 20
Users Last 7 days : 197
Users Last 30 days : 584