+251 11371 2982 aacracom@gmail.com

ቀዳማይ ልጅነትን ልማት ፕሮግራምን በተመለከተ

ፐሮግራሙ የከተማችንን 1.3 ሚሊዮን ህጻናትን በተለይ ደግሞ 330‚000 አነስተኛ ገቢ ካላቸው ቤተሰብ የተገኙ ህጻናት ለመድረስ ያለሙ አምስት አንኳር ኢኒሼቲቮሽን አቅደን ስንተገብር ቆይተናል።

👉ከተቀመጡት ግቦች አንጻር የወላጆችን እና አሳዳጊዎች የምክር እና የሙያ አገልግሎት የሚሰጡ 5‚000 ሰራተኞችን በማሰማራት በ 4‚979 የመኖሪያ ብሎኮች ለሚገኙ ለ 487,544 ወላጆች/አሳዳጊዎች በየአስራ አምስት ቀኑ የቤት ለቤት የምክር አገልግሎት ተሰጥቷል።

👉ለ11,900 አነስተኛ ገቢ ላላቸው እና ለድገት ውስኑነት ተጋላጭ የሆኑ ነፍሰ ጡር እና የሚያጠቡ እናቶች እንዲሁም ከ 3 ዓመት በታች ለሆኑ ህጻናት የቀጥታ አልሚ ምግብ ድጋፍ በየወሩ ተሰጥቷል።

👉ስራውን አጠናክሮ ለመቀጠል በዚህ በጀት አመትም ከ 5ዐዐ ሚሊየን በላይ በጀት ለአልሚ ምግብ በጅተናል፡፡

👉እድሜያቸው ከ 0 እስከ 3 ዓመት የሆኑ እና በኢኮኖሚ ሁኔታቸው ለዕድገት ውሱንነት ተጋላጭ የሆኑ ህጻናት የዕድገት ሁኔታ ፕሮግራሙ በተጀመረበት ወቅት ከነበረበት 66.9% ወደ 73.1% በማደግ የ 6.2 በመቶ መሻሻል አሳይቷል።

👉በጨዋታ መልክ በማስተማር በቅድመ አንደኛ ደረጃ ት/ቤቶች ይታይ የነበረው የትምህርት ዝግጁነት ምጣኔም ከነበረበት ዝቅተኛ ደረጃ ወደ 89.03% ከፍ በማለት የልጆች ሁለንተናዊ ዕድገት ማረጋገጥ ችለናል፡፡

Comments are closed.