+251 11371 2982 aacracom@gmail.com

ከተማ አሰተዳደሩ በ6 ወራት ህዝቡን የሰላም ባለቤት ከማድረግ አኳያ

👉በበጀት አመቱ 6 ወራት ህዝብን የሰላም ባለቤት ከማድረግ አኳያ፣ በርካታ ስራዎች ተሰርተዋል፡፡ ህዝቡ በሰላም ሰራዊት ተደራጅቶ አካባቢውን መጠበቅና ህገወጥ ድርጊቶችን የመከላከል ስራ አጠናክሮ ቀጥሏል፡፡

👉ከፌዴራልና ከአጎራባች ሸገር ከተሞች ጋር ጠንካራ ቅንጅታዊ አሰራር በመፍጠር የወንጀልና ህገ-ወጥ ድርጊቶችን በመከላከልና በመቆጣጠር የወንጀል ምጣኔ ከመቀነስ አኳያ ከህገ-ወጥ የጦር መሳሪያ ዝውውር፤ከህገ-ወጥ የገንዘብ ዝውውር ከኢኮኖሚ አሻጥር ከዝርፊያ ከሽብርና ደረቅ ወንጀሎች ጋር የተያያዙ ከ4687 በላይ የወንጀል ድርጊቶች ላይ የመከላከልና ህጋዊ እርምጃ የመውሰድ ስራ የተሰራ ሲሆን በት/ቤት ዙሪያና ከት/ት ተቋማት ውጭ የሚገኙና ለጸጥታ ስጋት በሆኑ 2919 አዋኪ ድርጊቶች ላይ እርምጃ በመውሰድ ተችሏል፡፡

👉በአጠቃላይ የአደባባይ ፕሮገራሞችና ኩነቶች በሰላም እንዲከበሩ ከማድረግ በተጨማሪ የከባድ ወንጀል ምጣኔ ከባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር በ33 በመቶ እንዲቀንስ ተደርጓል፡፡

የደንብ መተላለፍና ተያያዥ ህገ-ወጥ ተግባራትን በመከታተል፣ በመቆጣጠርና እርምጃ ከመውሰድ አንፃር 2464 ህገወጥ ግንባታዎች ላይ፣ 108 ህገ-ወጥ ንግድን፣ ህገ-ወጥ ደረቅና ፍሳሽ ቆሻሻ አያያዝና አወጋገድን መቆጣጠርና ደንብ ማስከበር ተችሏል።

ከንቲባ አዳነች አቤቤ

Comments are closed.