+251 11371 2982 aacracom@gmail.com

ውሃ አቅርቦትን አና የፍሣሽ ሥራዎችን በተመለከተ

👉የውሃ አቅርቦት ሥራዎችን በተመለከተ ነባር የመጠጥ ውሃ አቅርቦት በተያዘለት መርሃ ግብር መሰረት እየተከናወነ ሲሆን፣ባሳለፍናቸው 6 ወራት የተሰሩ አዳዲስ የመጠጥ ውሃ አቅርቦት በተመለከተ 15 የውሀ ጉድጓድ ቁፋሮ ተጠናቆ በቀን 25,000 ሜትር ኪዩብ ውሀ አቅርቦት ተጨምሯል ተጨማሪ ቀሪ 15 ጉድጓድ በቁፈሮ ላይ ይገኛል።

👉በተጨማሪ በቀን 100,000 ሜትር ኪዩብ የማምረት አቅም ያለው በኦሮሚያ ቡሾፍቱ አካባቢ የሚገኘው የጩቋላ ከርሠ ምድር የውሀ ልማት ፕሮጃክት 13 ጉድጓድ ሙሉ ለሙሉ ተጠናቆ በቀን 80,000 ሜትር ኪዩብ ውሀ ተገኝቷል።

👉7 ተጨማሪ ጉድጓድ በቁፈሮ ላይ ይገኛል እንዲሁም በቀን 73,000 ሜትር ኪዩብ የማምረት አቅም ያለው የገርቢ የውሃ ግድብ ፕሮጀክትን በከተማው በጀት ለመገንባት ወስነን ሂደት ላይ ይገኛል።

👉መሰረታዊ የአቅርቦት ችግር ለመፍታት ሁሉን አቀፍ የከርሠ ምድር ውሃ አጠቃቀምና አስተዳደር ጥናት (Comprensive ground water management project) በአለም አቀፍ አማካሪ ድርጅትእያስጠናን እንገኛለን፡፡

👉በቀን 30,000 ሜትር ኪዩብ ማጣራት የሚችል የቦሌ አራብሳ የፍሳሽ ማጣሪያ ጣቢያ ግንባታ ተጠናቋል በቀን 104,000 ሜትር ኪዩብ ማጣራት የሚችል የምስራቅ ተፋሰስ የፍሳሽ ማጣሪያ ጣቢያ ግንባታ ተጀምሯል።

👉በቀን 20,000 ሜትር ኪዩብ ማጣራት የሚችል የኮዪ ፈጬ 1 እና 2 የፍሳሽ ማጣሪያ ጣቢያ ግንባታ ተጀምሯል፡፡ ለረጅም ዘመናት ብክለትን በማስከተል እና የጤና ጠንቅ በመሆኑ ሲያስቸግሩ የኖሩ የወንዝና ወንዝ ዳርቻ 23.6 ኪ. ሜትር የማጽዳትና የመንከባከብ ስራ ተሰርቷል።

👉 ከዚህ በተጨማሪ ፍሳሽን ወደ ወንዞች በመልቀቅ ብክለት ማስከተልን የሚከላከል ደንብ በካቢኔዎች ፀድቆ በመተግበር ላይ ይገኛል፡፡

ከንቲባ አዳነች አቤቤ

Comments are closed.