+251 11371 2982 aacracom@gmail.com

ባለፉት 6 ወራት በስራ ዕድል ፈጠራ የተመዘገቡ ዉጤታማ አፈፃፀሞች ማሳያ፤-

👉150,000 የስራ እድል ለመፍጠር እቅድ ተይዞ ለ142,908 ቋሚ የስራ ዕድል መፍጠር ተችሏል።

👉በዘርፍ ከፋፍለን ስንመለከት 97,126 (68%) የስራ ዕድል የተፈጠረዉ በአገልግሎት ዘርፍ ሲሆን በኢንዱስትሪ ዘርፍ 30,606(21%) የስራ ዕድል ተፈጥሯል፡፡

👉በከተማ ግብርና ዘርፍ 15 ሺ112(11%) የስራ ዕድል ተፈጥሯል፤በዚህም የሴቶች ድርሻ 76,107 (53.3%) ነዉ፡፡

👉በኢንዱስትሪ ልማት ዘርፍ ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ ዋናው የትኩረት ነጥብ የአምራች ኢንዱሰትሪዎችን አቅም ማጎልበትና አምራች ኢንዱስትሪው የሚያነሱትን የመሰረተ ልማት ጥያቄዎችን የመፍታት ስራ ተሰርቷል፡፡

👉 ከዚህም አኳያ የመብራት፤የውሀ እና የመንገድ ችግር የነበረባቸውን ኢንዱስትሪዎች በመለየት መብራት 231 ኢንዱስትሪዎች ችግራቸውን መፍታት ተችሏል፡፡

👉በተመሳሳይ የካታል ሊዝ አቅርቦት ለ276 ኢንዱስትሪዎች በማቅረብ እቅዱን ማሳካት ተችሏል፡

👉184 ኢንዱስትሪዎች ምርታቸውን ወደ ውጪ እንዲልኩ በማድረግ 1,671 አምራች ኢንዱስትሪዎች 725,480,810 ቶን ተኪ ምርት በማምረት 490,630,180 ዶላር የውጪ ምንዛሪ ማዳን ችለዋል፡፡

ከንቲባ አዳነች አቤቤ

Comments are closed.