+251 11371 2982 aacracom@gmail.com

አስተዳደሩ በጃፓን ድጋፍ የተገዙ 79 ማሽኖችን ተረከበ

አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 4፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የጃፓን መንግስት በሰጠው ድጋፍ የተገዙ 79 ለመንገድ ጥገና የሚያገለግሉ ማሽኖችንና ከባድ ተሽከርካሪዎች መረከቡን አስታወቀ፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ÷ “ለከተማችን ሁሉን አቀፍ ልማት የላቀ ፋይዳ ያላቸውን ዘመናዊ ሰፋፊ መንገዶችን እየገነባንና እያሰፋን ባለንበት ወቅት የተደረገልን ድጋፍ ትልቅ ፋይዳ አለው” ብለዋል::

የጃፓን መንግስት እና ሕዝብ እንዲሁም የጃፓን ዓለም አቀፍ ትብብር ኤጀንሲ ላደረጉልን ድጋፍ በከተማ አስተዳደራችን ስም እናመሰግናለን ሲሉ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ገልጸዋል፡፡

#Ethiopia

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/

ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting

ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/

ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision

ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/

ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

Comments are closed.